ሕዳሴ አኩሪ ገድል የሚዘከርበት የአሸናፊነት ብራና ነው።

7

ባሕር ዳር፡ መስከረም 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ)የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ተከትሎ በሰሜን ሸዋ ዞን በሲያደብርና ዋዩ ወረዳ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።

የሰሜን ሸዋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ኤልያስ አበበ ሕዳሴ የአሸናፊነት ማሳያ፣ የብልጽግና ጉዞ ማብሰሪያ እና በአንድነት ማሳካት የማንችለው እንደሌለ ያሳየ ዳግማዊ ዓድዋ ነው ብለዋል።

በኅብረት የማንችለውና የማናሳካው አይኖርም ያሉት ኀላፊው በኅብረት ችለናል፤ ዓባይ የብልጽግናችን ጅማሮ ነው፤ በቀጣይም በርካታ ሥራዎችን እንሠራለን ነው ያሉት።

ከሰሜን ሸዋ ዞን ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው የዚህ ዘመን ትውልድ አኩሪ ገድል የሚዘከርበት የአሸናፊነት ብራና ነው ተብሏል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous article“የድጋፍ ሰልፉ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ ተጠናቅቋል” የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ
Next article“ግድቡ ከደብተር እና ስክብሪቶ መግዣየ ቀንሼ የደገፍኩት ትልቅ ስጦታየ ነው” ተማሪ ፋሲካ