“ፈጣሪ ለዚህ ስላበቃን እናመሰግነዋለን” ብጹዕ አቡነ ኤርሚያስ

5

ወልድያ: መስከረም 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ) “የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የማንሠራራት ምልክት ነው” በሚል መሪ መልዕክት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መመረቅን አስመልክቶ በወልድያ ከተማ የደስታ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል።

የሰሜን ወሎ ዞን ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የቅዱስ ላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት የበላይ ጠባቂ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብጹዕ አቡነ ኤርሚያስ በዕለቱ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዓባይ እንዲገደብ አባቶቻችንን ያነሳሳ፤ እኛ ልጆቻቸው እንድንፈጽመው ላበረታን እግዚአብሔር ይመስገን ብለዋል ብጹዕነታቸው።

ኢትዮጵያን ለማበልጸግ ሲያስቡ ዓባይን መገደብ ወሳኝ መኾኑ ታያቸውና አቀዱ ብለዋል። ከፍጻሜ ሳያደርሱት አለፉ ነው ያሉት። እኛ ልጆቻቸው ዕቅዳቻውን ተረክበን በእኛው ገንዘብ፣ በእኛው ጉልበት፣ በእኛው ዕውቀት ዕቅዳቸውን ለፍጻሜ አበቃን ነው ያሉት።

ሀገራችን ሳንሰጣት አትሰጠንምና፣ ሳናሳድጋትም አታሳድገንምና ቀሪ ሥራዎችን በአንደነት እና በፍቅር ተባብረን ልንሠራ ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።

“ፈጣሪ ለዚህ ስላበቃን እናመሰግነዋለን” ብለዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአይችሉምን ትርክት የሰበረ የኩራታችን ምንጭ ነው።
Next article“የድጋፍ ሰልፉ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ ተጠናቅቋል” የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ