ግድቡን ማጠናቀቅ የአሸናፊነት ድል አክሊል መድፋት ነው።

10

ባሕር ዳር፡ መስከረም 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ)የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ በሰሜን ሸዋ ዞን ሀገረማርያም ከሰም ወረዳ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።

በሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፉ የተለያዩ መልዕክቶች ተላልፈዋል።

👉 ግድባችን ተጠናቅቋል፤ የጠላቶቻችን ሴራ በኢትዮጵያዊ አርበኝነት እሳት ተቃጥሎ ከስሟል።

👉 ግድባችን ለተፋሰሱ ሀገራት በረከት እንጂ ጉዳት አያመጣም።

👉የውጭ ተጽዕኖ ያልበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነት ላይ የቆመ ግድብ።

👉 ግድቡን ማጠናቀቅ የአሸናፊነት ድል አክሊል መድፋት ነው።

👉 ግድባችን የዓባይ ዘመን ትውልድ የተጋድሎ ሰንደቅ።

👉 ግድባችን የይቻላል መንፈስ እርሾ የቁጭት ታሪካችን ማብሰሪያ ታሪክ ነው።

👉 ግድባችን በራሳችን አቅም የገነባነው የአንድነታችንና የአብሮነታችን ምሰሶ ነው የሚሉ እና ሌሎች መልዕክቶች መተላለፋቸውን ከሰሜን ሸዋ ዞን ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleግድቡ በኢትዮጵያዊነት ኅብር ፀንቶ የመቆም የአሸናፊነት ኒሻን ነው።
Next articleታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአይችሉምን ትርክት የሰበረ የኩራታችን ምንጭ ነው።