ግድቡ በኢትዮጵያዊነት ኅብር ፀንቶ የመቆም የአሸናፊነት ኒሻን ነው።

21

ባሕር ዳር፡ መስከረም 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ)የታላቁን የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ በሰሜን ሸዋ ዞን መንዝ ጌራ ምድር ወረዳ እና መሐል ሜዳ ከተማ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።

በሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፉ የተለያዩ መልዕክቶች ተላልፈዋል።

👉 ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን የአይቻልም መንፈስን የሰበርንበት ዳግም የዓድዋ ድል ነው።

👉የሕዳሴ ግድባችን እኛ ኢትዮጵያውያን ወደ ዳግም ትንሳኤ የምንሸጋገርበት ልዩ ፀጋችን ነው።

👉 የሕዳሴ ግድብ የብልጽግናችን አሻራ ነው።

👉 በግድቡ የተባበረ ክንድ ለብልጽግናችን ይተጋል።

👉ግድባችን የዓባይ ዘመን ትውልድ ትክክለኛ ሀሳብ፣ በትክክለኛ ጊዜ የገነባው ዘመን ተሸጋሪ ቅርስ ነው

👉 ግድባችን በኢትዮጵያዊነት ኅብር ፀንቶ የመቆም አሸናፊነታችን ኒሻን ነው የሚሉ እና ሌሎች
መልዕክቶች መተላለፋቸውን ከሰሜን ሸዋ ዞን ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleየሕዳሴ ግድብ በራስ አቅም የተገነባ የአንድነት እና የአብሮነት ውጤት ነው፡፡
Next articleግድቡን ማጠናቀቅ የአሸናፊነት ድል አክሊል መድፋት ነው።