ታሪክ መሥራታችንን እንቀጥላለን።

2

ባሕር ዳር፡ መስከረም 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ)የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ተከትሎ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በምዕራብ ደምቢያ ወረዳ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።

የምዕራብ ደምቢያ ወረዳ ዋና አሥተዳዳሪ አስፋው አዱኛ ለብዙ ዘመናት በዓባይ ላይ ሳንጠቀምበት ቆይተናል ብለዋል። አሁን ደግሞ ከብዙ ውጣ ውረዶች በኋላ ተጠናቅቆ ለመመረቅ በመብቃቱ እንኳን ደስ ያለን ነው ያሉት።

የሕዳሴ ግድብን በራስ አቅም ገንብተን ለምርቃት እንዳበቃነው ሁሉ ከሕዝቡ ጋር ሆነን ታሪክ መሥራታችንን በተግባር እናሳያለን ብለዋል።

‎ከምዕራብ ደምቢያ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው በድጋፍ ሰልፉ የታደሙ ሠልፈኞችም የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ በመመረቁ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!


Previous article“ሕዳሴው ግድብ ተጠናቅቆ በማየታችን ዳግም የተወለድን ያህል ነው የተሰማን” የድጋፍ ሰልፈኞች
Next article“ታሪካዊ ጠላቶቻችን ዓባይን እንደበረከት ሳይኾን እንደ እርግማን እንድናየው አድርገውን ኖረዋል”