የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ማንሰራራት ምልክት ነው።

2

ጎንደር፡ መስከረም 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የ‎ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ ‎በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ላይ አርማጭሆ ወረዳ ትክል ድንጋይ ከተማ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

በሰልፉ ላይ የተለያዩ መልዕክቶች የተላለፉ ሲኾን ከመልዕክቶቹ መካከልም፦

👉‎ግድባችን በራስ አቅም እና በአፍሪካዊነት ኩራት የተገነባ ነው።

👉‎የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ማንሰራራት ምልክት ነው።

👉‎የሕዳሴ ግድብ የብልጽግናችን አሻራ ነው።

👉‎የሚደገም ድል፣ የሚጨበጥ ብስራት የሕዳሴ ግድብ ‎የሚሉ እና መሰል መልዕክቶች በድጋፉ ሰልፉ ተላልፈዋል።

‎በድጋፍ ሰልፉ የወረዳው ነዋሪዎች እና የሥራ ኀላፊዎች ተሳታፊ ኾነዋል።

ዘጋቢ፦ ‎ቃልኪዳን ኃይሌ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleየታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይኾን የአፍሪካ ኩራት እንደኾነ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።
Next articleአሸንፈን አፍሪካን አኩርተናል ዓለምንም አስደምመናል።