የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መመረቅን ምክንያት በማድረግ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ደስታቸውን በሰላማዊ ሰልፍ እየገለጹ ነው።

1

ጎንደር፡ መስከረም 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መመረቅን ምክንያት በማድረግ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ደስታቸውን በሰላማዊ ሰልፍ እየገለጹ ይገኛሉ።

ሰልፈኞቹ ከየክፍለ ከተማው የመጡ ሲኾን የተለያዩ መልዕክቶችን እያስተላለፉ ነው።

ካስተላለፏቸው መልዕክቶች መካከልም፦

👉ግድባችን የመነሳት ደወል ብሥራት የኢትዮጵያ ድምቀት

👉የውጭ ተጽዕኖ ያልበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነት ላይ የቆመ ግድብ

👉የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ምልክት

👉የህዳሴ ግድብ! የብልጽግናችን አሻራ

👉ግድባችን የመቻል ማሳያ የማንሰራራት ጅማሮ ምልክት

👉 የሚደገም ድል፣ የሚጨበጥ ብስራት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና ሌሎችም መልዕክቶችን እያሰሙ ነው።

ዘጋቢ፦ ያየህ ፈንቴ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleየታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ተከትሎ በባሕርዳር ከተማ የደስታ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
Next articleየታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መመረቅን አስመልክቶ ሰላማዊ ሰልፍ በሰቆጣ ከተማ እየተካሄደ ነው።