በደሴ ከተማ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ ተጀምሯል። 

1

ደሴ: መስከረም 05/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የመማር ማስተማር ሂደቱ በከተማ አሥተዳደሩ በሚገኙ በ122 የመንግሥት እና የግል ትምህርት ቤቶች በይፋ መጀመሩን ነው የከተማ አሥተዳደሩ ትምህርት መምሪያ ኀላፊ ፍቅር አበበ የተናገሩት።

 

በከተማ አሥተዳደሩ 62 ሺህ 100 ተማሪዎች ለመማር መመዝገባቸውንም አቶ ፍቅር አስታውሰዋል።

 

ከአሚኮ ጋር ቆይታ የነበራቸው ወላጆች በመጀመሪያ ቀን ልጆችን ወደ ትምህርት ቤት መውሰድ ልዩ ትዝታ እንዳለው ገልጸዋል።

 

የከተማችን ሰላም በመረጋገጡ ልጆቻችን ለአፍታም ከትምህርት ገበታ ተነጥለው አያውቁም ያሉት የተማሪ ወላጆች ለትምህርት ስኬት ሁሉም በጋራ እንዲሠራ ጠይቀዋል።

 

ዘጋቢ፦ ደምስ አረጋ

 

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

👇👇👇

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

 

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየ2018 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ በደብረ ማርቆስ ከተማ ተጀመረ።
Next articleበደብረ ብርሃን ከተማ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ዛሬ የመማር ማስተማር ሥራ ተጀምሯል።