“ጎንደር ከጉስቁልና ወጥታ እያንሠራራች ነው” ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው 

4

ጎንደር: ጳጉሜን 04/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ጳጉሜን 04 የማንሠራራት ቀን በማስመልከት በጎንደር ከተማ አሥተዳደር እየተሠሩ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች አና የከተማዋ ነዋሪዎች እንዲኹም የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች ጎብኝተዋል።

 

በመርሐ ግብሩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኛው ጎንደር ከነበረችበት እና ከተገታው እድገቷ በልጆቿ ትብብር ወደ ቀድሞ ክብሯ እየተመለሠች መኾኗን ተናግረዋል። ጎንደር ከከተሜነት ታሪኳ ጋር አብሮ የማይሄድ ጉስቁልናዋ አብቅቶ የሕዳሴዋ ዘመን ላይ ስለመኾኗም አብራርተዋል።

 

የዛሬው ቀን አባይ የተገደበበት ቀን በመኾኑ ጭምር ልዩ ያርገዋል ያሉት አቶ ቻላቸው ይህ የማንሠራራት ዘመን እንዲቀጥል ሕዝቡ ከመንግሥት ጎን በመቆም ጉልበት እንዲኾንም ጠይቀዋል።

 

በጉብኝቱ የተገኙት መልዓከ ገነት ቄስ ፈንታ ገብረ ሚካኤል የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ውበት ያስጠበቀ እና ለሥራ ፈላጊዎችም የሥራ ዕድል የፈጠረ በመኾኑ ደስተኛ መኾናቸውን ነው የገለጹት።

 

ሌላው በጉብኝቱ የተገኙት የሀገር ሸማግሌ አስረስ መሐመድ ከዚህ በፊት የቆሻሻ መጣያ የነበረ ቦታ በዚህ መልኩ ውብ ኾኖ በማየታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። ልማቱ መቀጠል አንዳለበትም አንስተዋል።

 

ዘጋቢ:- ማርታ አዱኛ

 

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

👇👇👇

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

 

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የዘመኑ ትውልድ የጋራ እና የወል እውነት መኾኑን ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ተናገሩ። 
Next articleየአማራ ክልል ምክር ቤት እና በአማራ ክልል የሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጋራ ለመሥራት የስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ።