አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሆኑ፡፡

375

ባሕር ዳር፡ ሰኔ 02/2012 ዓ.ም (አብመድ) የቀድሞው የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በድጋሚ በቃል አቀባይነት ተሹመዋል፡፡

ኢትዮጵያን በተለያዩ ሀገራት በአምባሳደርነት ያገለገሉት ዲና ሙፍቲ ከውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ከወጡ በኋላ በኬንያ እና ግብጽ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው አገልግለዋል፤ በቅርቡ ደግሞ ወደ ሀገር ቤት ተመልሰዋል፡፡

አብመድ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ደግሞ አምባሳደር ዲና በድጋሚ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሆነው ተሹመዋል፡፡

Previous articleበአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓታት በ10 ሰዎች ላይ የኮሮናቫይረስ ተገኘባቸው፤ በ24 ሰዓታት ውስጥ ያገገምም ሆነ ሕይወቱ ያለፈ ሰውም የለም፡፡
Next articleሱዳን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ድርድር እንደገና እንዲጀምር ጥሪ አቀረበች፡፡