በሕዳሴ ግድቡ ውኃ ለመያዝ የሚያስችሉ ሥራዎች ከሳምንታት በኋላ እንደሚጠናቀቁ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ገለጹ።

221

በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ውኃ ለመያዝ የሚያስችሉ ሥራዎች ከሳምንታት በኋላ እንደሚጠናቀቁ የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ገልጸዋል።

በቀጣይ ሳምንታት ቀሪ ተግባራትን በማከናወን ግድቡ የመጀመሪያውን ዙር ውኃ መያዝ እንደሚችል ሚኒስትሩ መግለጻቸውን ኢብኮ ዘግቧል። ይህም በሚቀጥለው ዓመት የቅድመ-ኃይል ማመንጫ ተግባሩን ለማከናወን ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ነው ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ የተናገሩት።

በኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የተመራ ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች ልዑክ ዛሬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን የግንባታ ሂደት መጎብኘቱ ይታዎሳል።

የልዑኩ አባላት ከጉብኝታቸው በኋላ ግድቡ በሚገነባበት አካባቢ ችግኝ መትከላቸውም ታውቋል።

Previous articleበአማራ ክልል የኮሮናቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 119 መድረሱን የክልሉ ጤና ቢሮ ገለጸ።
Next articleበኢትዮጵያ ተጨማሪ 86 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው፤ ሰባት ተጨማሪ ሰዎች ሕይወትም አልፏል፡፡