መርዓዊ ከተማ ሰላሟን ከማስጠበቅ ጎን ለጎን ስታከናውናቸው የነበሩ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን እያስመረቀች ነው።

20

ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 27/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በሰሜን ጎጃም አሥተዳደር ዞን በመርዓዊ ከተማ የተገነቡትን እና እድሳት የተደረገላቸውን ቢሮዎች እና የአገልግሎት መስጫ ተቋም እየተመረቁ ነው።

ከሚመረቁ ልማቶች ውስጥ የከተማ አሥተዳደሩ የከንቲባ ጽሕፈት ቤት፣ የፖሊስ ጽሕፈት ቤት፣ የብልጽግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት፣ መናኸሪያ አገልግሎት ይገኝበታል።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ በምሥራቅ ዕዝ የ304ኛ ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል አዲሱ መሐመድ፣ የሰሜን ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አሰፋ ጥላሁን፣ የሰሜን ጎጃም ዞን ብልጽግና ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ማስተዋል አሰሙ እና ሌሎችም ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleመሠረተ ልማቶች ዘላቂ ጥቅም እንዲሰጡ ኅብረተሰቡ ተገቢውን ጥበቃ ሊያደርግ ይገባል።
Next articleየኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ምክር ቤት ጉባኤ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።