በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ሁሉም በንቃት እንዲሳተፍ አቶ አደም ፋራህ ጥሪ አቀረቡ።

18

ባሕር ዳር: ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር መሠረታዊ ጥያቄያችንን የሚመልስ እና ከሀገር አልፈን ለዓለም የምንተርፍበት ንቅናቄ ነው ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኀላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ገልጸዋል፡፡

አቶ አደም ፋራህ በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በጅግጅጋ ከተማ ችግኝ ተክለዋል፡፡

በአረንጓዴ አሻራ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋፋት እንዲሁም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰድን ነው ብለዋል፡፡

በየዓመቱ የራሳችንን ሪከርድ ያሻሻልንበት የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር፣ ከሌሎች ሳንጠብቅ በራስ ተነሳሽነት ምሳሌ የኾንበት ነው ያሉት አቶ አደም ፋራህ በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ሁሉም በንቃት እንዲሳተፍም ጥሪ አቅርበዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleከ1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገበት የወሎ ኮምቦልቻ የመንገደኞች አውሮፕላን ማረፊያ ማስፋፊያ ተመረቀ።
Next articleተፈጥሮን መጠበቅ የትውልድ አደራ ነው።