
ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር የአረንጓዴ አሻራ አርበኞች አሻራቸውን ለማሳረፍ ወደ ችግኝ መትከያ ቦታዎች እየተመሙ ነው።
የአረንጓዴ አሻራ አርበኞች የሚተከሉ ችግኞችን በመያዝ ወደተዘጋጀው ተፋሰስ እያመሩ ነው።
የችግኝ ተከላው በሰቆጣ ከተማ አማኑኤል መውጫ ላይ ባለው ቦታ ነው የሚከናወነው።
ዘጋቢ፦ ደጀን ታምሩ ከሰቆጣ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን