የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በበጀት ዓመቱ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ግማሽ ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል እየሠራ ነው።

9

አዲስ አበባ፡ ሐምሌ 19/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቤ ሳኖ፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ በአዲስ አበባ የሚገኙ የንግድ ባንክ ዲስትሪክት ሥራ አሥኪያጆች እና የባንኩ ባለሙያዎች በዋናው መሥሪያ ቤት እና በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ አረንጓዴ አሻራቸውን አስቀምጠዋል።

ፕሬዝዳንቱ አቤ ሳኖ በዛሬው መርሐ ግብር 35 ችግኞች በዋናው መሥሪያ ቤት እና በቦሌ ለሚ ኢንዱሰትሪ ፓርክ ደግሞ 20 ሽህ ችግኞችን ተተክለዋል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ በመላ ሀገሪቱ በሁሉም የንግድ ባንክ ሠራተኞች ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታ ያላቸዉን ግማሽ ሚሊዮን ችግኞችን እንተክላለን ብለዋል።

ችግኝ መትከል የአየር ንብረት ለዉጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም ሚናዉ የጎላ መሆኑን የተናገሩት ፕሬዘዳንቱ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄው ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግና የተከሉ ችግኞችም ጸድቀዉ ለተፈለገዉ ዓላማ እስኪድረሱ መንከባከብ እንደሚገባ መክረዋል።

ዘጋቢ፦ በለጠ ታረቀኝ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በበጀት ዓመቱ 1 ሺህ 210 ኪሎሜትር የመንገድ ፕሮጄክቶች ተሠርተዋል” ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ
Next article“ዋነኛ የኢኮኖሚ ምንጭ ለኾነው ግብርና ትኩረት መስጠት ይገባል” ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ