
ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 18/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በሕክምና ዘርፍ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው።
በምረቃ መርሐ ግብሩ የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የድንገተኛ ጤና አደጋ ስጋት ምላሽ ማስተባበሪያ ኀላፊ ዶክተር መልካሙ አብቴ ጨምሮ ሌሎች እንግዶች እና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ዛሬ እየተመረቁ የሚገኙት ተማሪዎች በሕክምና ዶክትሬት ዲግሪ እና በእንስሳት ሕክምና ዘርፍ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ናቸው።
ዘጋቢ፡- አሰፋ ልጥገበው
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን