በዚህ ክረምት አምስት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ያለመው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ዛሬ ይጀመራል፡፡

736

ባሕር ዳር፡ ግንቦት 28/2012 ዓ.ም (አብመድ) የዚህ ዓመት የአረንጓዴ አሻራ ቀን ዛሬ ዓርብ ግንቦት 28/2012 ዓ.ም ይጀመራል፡፡

መርሀ ግብሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሀዋሳ ላይ ይጀመራል። በአማራ ክልል ደግሞ በሰሜን ሜጫ ወረዳ የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር ተመሥገን ጥሩነህ ያስጀምራሉ። በሌሎች ክልሎችም ዛሬ መርሀ ግብሩ እንደሚጀመር ይጠበቃል።

ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ሐምሌ 22/2011ዓ.ም በተካሄደው ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ ቀን 200 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀምበር ለመትከል አቅዳ ከ353 ሚሊዮን በላይ ችግኝ በመትከል አዲስ ክብረወሰን ማስመዝገቧ የሚታወስ ነው፡፡

በክብረ ወሰንነት ተይዞ ከነበረው ከአምስት እጥፍ በላይ መሆኑም የሚታወስ ነው፡፡ ከዚያ በፊት በህንድ ተይዞ የነበረውን በአንድ ጀምበር በ800 ሺህ በጎ ፈቃደኞች ከ50 ሚሊዮን በላይ ችግኝ የመትከል ክብረ ወሰን ኢትዮጵያ በብዙ ርቀት አሻሽላዋለች፡፡

ዘንድሮ ደግሞ በክረምት ወቅቱ በሚኖረው የአረንጓዴ አሻራ ወቅት 5 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ነው የታቀደው፡፡

Previous articleየጣና ሐይቅን ኅልውና ለማረጋገጥ በጥናት ተመሥርቶ በቅንጅት መሥራት ላይ እንዲተኮር የክልሉ መንግሥት አሳሰበ።
Next articleአዲሱ የመሬት ካሳ ክፍያ መመሪያ ጸድቆ ወደ ተግባር አለመግባት በኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ ባለሀብቶች ከፍተኛ እንቅፋት መፍጠሩን በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶች እና ተቋማት ገለፁ፡፡