የኢትዮጵያ ብር በሩሲያ የባንክ ምንዛሬ ውስጥ ተካተተ። የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ የኢትዮጵያን ብር በምንዛሬ ዝርዝር ውስጥ አካቷል።

37

ባንኩ ለ100 የኢትዮጵያ ብር 57 ነጥብ 5872 ሩብል ወይም ለ1 ብር 0 ነጥብ 575872 ሩብል የምንዛሬ ተመን አስቀምጧል።

ባንኩ ለኢትዮጵያ ብር ምንዛሬ ተመን የኮድ ቁጥር 230 የሰጠ ሲሆን በየዕለቱም የምንዛሬ ተመኑን የሚያሳውቅ ይሆናል።

የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ የኢትዮጵያን ብር ጨምሮ የ12 ሀገራት ገንዘቦች ከሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ጋር ያላቸውን ይፋዊ የምንዛሪ ተመን ለማስቀመጥ ውሳኔ ላይ መድረሱን ከቀናት በፊት ይፋ አድርጎ ነበር።

Previous articleበተጠናቀቀው በጀት ዓመት ውጤታማ ሥራዎች ተሠርተዋል።
Next articleበደብረ ማርቆስ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውኃን ተደራሽነት ለማሳደግ እየተሠራ ነው።