ክልሉን የልማት ማዕከል ለማድረግ ለሰላም እንደሚቆሙ በአዋበል ወረዳ የወጀል ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

9

ባሕርዳር፡ ሰኔ 27/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ‎‎ ”ሰላም ለሁሉም፣ ሁሉም ለሰላም” በሚል መሪ መልዕክት በምሥራቅ ጎጃም ዞን በአዋበል ወረዳ የወጀል ከተማ ነዋሪዎች ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እያካሄዱ ነው።

በሰላማዊ ሰልፉ ሰላሜን እጠብቃለሁ ብልጽግናየን አረጋግጣለሁ፣ ሰላምን እንሻለን፣ ክልላችንን የሰላም እና የልማት ማዕከል ለማድረግ ሁላችንም ለሰላም ዘብ እንቆማለን፣ ጽንፈኝነትን እናወግዛለን፣ ከመንግሥት ጎን እንቆማለን፣ መንግሥት ሕግን በማስከበር የዜጎችን ሰላም ሊያስጠብቅ ይገባል የሚሉ እና ሌሎች መልዕክቶች እየተላለፉ ይገኛሉ። ከምሥራቅ ጎጃም ዞን ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው መንግሥት እየወሰደ ያለውን እርምጃ እንደሚደግፉም ገልጸዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleዘላቂ ሰላምን ለማጽናት እና የልማት እንቅስቃሴዎችን ለማጠናከር ዓላማ ያደረገ ውይይት ከወረኢሉ ከተማ እና ወረዳ ነዋሪዎች ጋር እየተካሄደ ነው።
Next articleየተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ጤና ተቋማት እውቅና ተሰጥቷል።