የውጭ ሀገር ሥራ ሥምሪት ረቂቅ አዋጅ የዜጎችን መብት፣ ደኅንነት እና ዘላቂ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው።

16

ባሕር ዳር: ሰኔ 16/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በውጭ ሀገራት የሚሠሩ ኢትዮጵያውያንን መብት፣ ደኅንነት እና ዘላቂ ጥቅም ያስጠብቃል ያለውን የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ረቂቅ አዋጅ አዘጋጅቶ አቅርቧል፡፡

ረቂቅ አዋጁ ግንቦት 21/2017 ዓ.ም ለሚኒስትሮች ምርቤት ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ መወሰኑ ይታወቃል፡፡የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ረቂቅ አዋጁን መርምሮ ሰኔ 5/2017 ዓ.ም ለሰው ኃይል ሥራ ሥምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል፡፡ ረቂቅ አዋጁ ሲጸድቅ የዜጎችን መብት፣ ደኅንነት እና ዘላቂ ተጠቃሚነት ያረጋግጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ደረጃ ያለው የፍቃድ አሰጣጥ ሥርዓት፣ የተቀነሰ የገንዘብ ዋስትና፣ ጥብቅ የፋይናንስ ቁጥጥሮች፣ ግልጽ እና ከሰው ንክኪ ነፃ የኾነ የአሠራር ሥርዓት የረቂቅ አዋጁ ቁልፍ ማሻሻያዎች መኾናቸው ተጠቅሷል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleየትምህርት ቤቱን ሀገር አቀፍ ውጤታማነት ለማስቀጠል መዘጋጀታቸውን የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ተናገሩ።
Next articleየዜጎችን የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየሠራ መኾኑን የደብረ ማርቆስ ከተማ አሥተዳደር አስታወቀ።