ከመላው ኢትዮጵያ የተውጣጡ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የባሕር ዳር ከተማን የልማት ሥራዎች ጎበኙ።

10

ባሕር ዳር: ሰኔ 10/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ከተለያዩ ክልሎች እና የሀገሪቱ አካባቢዎች የተውጣጡ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ባሕር ዳር ከተማ ገብተዋል። ባለሙያዎች ባሕር ዳር ከተማ ሲደርሱ የከተማ አሥተዳደሩ መሪዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የባሕር ዳር ከተማን የልማት ሥራዎች ተዘዋውረው ተመልክተዋል። በጣና ሐይቅ ላይ የሚገነባውን ጣና ማሪና ሪዞርት፣ አዲሱን የዓባይ ድልድይ፣ የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም፣ የኮሪደር ልማት እና ሌሎችንም የልማት ሥራዎች ነው ተዘዋውረው የተመለከቱት።

ባለሙያዎች ባሕር ዳር ከተማ ሰላሟን አሥጠብቃ እየለማች የምትገኝ የቱሪዝም ከተማ መኾኗን በጉብኝታቸው ወቅት ገልጸዋል።

ዘጋቢ:- ዳግማዊ ተሠራ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleጊዜያዊ የረዥም ጊዜ /የኮንትራት/ ቅጥር ማስታወቂያ
Next article“ክልሉ ወደ ተረጋጋ ኹኔታ እንዲመጣ የሴት መሪዎች ሚና ከፍተኛ ነበር” አቶ ይርጋ ሲሳይ