
ባሕር ዳር: ሰኔ 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የፌደራል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች በባሕር ዳር ከተማ የተሠሩ የልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ነው።
በጉብኝቱ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እና ሚኒስትሮች ተገኝተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት የአማራ ክልል የሥራ ኀላፊዎች እና የባሕር ዳር ከተማ ሕዝብ ለክቡር የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ላደረጋችሁት ደማቅ አቀባበል አመሰግናለሁ ነው ያሉት።
“ባሕር ዳር ተፈጥሮ እና የሰው ጥበብ ሲሠናኙ ምን ሊፈጥሩ እንደሚችሉ እያሳየች ነው” ብለዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!