የሰሜን ወሎ ዞን ሲቪል ሰርቪስ መምሪያ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ማጣራት ሥራ መጀመሩን ገለጸ።

20
ወልድያ: ሰኔ 07/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የሰሜን ወሎ ዞን ሲቪል ሰርቪስ መምሪያ የ11 ወራት የሥራ አፈፃፀሙን ገምግሟል። የዞኑ ሲቪል ሰርቪስ መምሪያ ኀላፊ ሙሉ አዲሴ መንግሥት ሠራተኞች ባለፉት 11 ወራት በጸጥታ ችግር ውስጥም ኾነው የሕይወት መስዋዕትነት እየከፈሉ ኅብረተሰቡን ማገልገላቸውን ጠቅሰዋል።
ሕዝብን በማገልገል እና ሰላምን በማስፈን ረገድ ጉልህ ድርሻ መወጣታቸውንም ነው ያስረዱት።በተለይም የሰው ኀይል ስምሪቱ በውድድር ሕጉ እንዲፈጸም በልዩ ሁኔታ እየተገመገ መመራቱን ገልጸዋል።
ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ማጣራት ሥራ ተጀምሯል ብለዋል ኀላፊዋ። ሀሰተኛ የሥራ ልምድ፣ የሕክምና ማስረጃ እና የደኅንነት ስጋት ማስረጃዎችም የማጣራት ሥራ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
ሁሉም የወረዳዎች እና ከተማ አሥተዳደሮች ሲቪል ሰርቪስ ጽሕፈት ቤት ኀላፊዎች እና ቡድን መሪዎች በግምገማ መድረኩ ተገኝተዋል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን
Previous articleለደብረ ብርሃን ከተማ የመንግሥት ሠራተኞች የሕፃናት ማቆያ ማዕከል ለመገንባት የመሰረተ ድንጋይ ተቀመጠ።
Next articleየጤና አጠባበቅ ጣቢያዎችን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል እየሠራ መኾኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን አስታወቀ።