ለርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የሜዳሊያ ሽልማት ተበረከተ።

34

ባሕር ዳር: ሰኔ 05/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕር ዳር ከተማ ሲካሄድ የነበረው ሦስተኛው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሀገር አቀፍ ኮንፈረንስ ተጠናቅቋል።

በጉባኤው የማጠቃለያ ዝግጅት ላይ የተለያዩ አካላት ዕውቅና እና ምሥጋና አግኝተዋል።

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ለክልሉ እና ለሀገር ሰላም ጠንካራ ሥራዎችን እያከናወኑ መኾኑ እና በተለይም በአማራ ክልል ተከስቶ የነበረው ግጭት ተፈትቶ አንጻራዊ ሰላም እንዲመጣ አበርክቷቸው የላቀ እንደነበር ተመላክቷል።

ሦስተኛው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሀገር አቀፍ ኮንፈረንስ በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወንም ርእሰ መሥተዳድሩ ከፍተኛ አበርክቶ እንደነበራቸው ተጠቅሶ ለዚህም አገልግሎታቸው የሚመጥን ሜዳሊያ ተሸልመዋል።

ሜዳሊያውን የጉባኤው የበላይ ጠባቂ ታላላቅ የሃይማኖት አባቶች አበርክተውላቸዋል።

ዘጋቢ፦ አሚናዳብ አራጋው

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous article“ቀኑ ፈጽሞ ሳይመሽ ሃይማኖትን ከፖለቲካ፣ ፖለቲካን ከሃይማኖት ሳንቀይጥ ለሰላም እንቁም” ብጹዕ አቡነ አብርሃም
Next article“ሰላም በምድሪቱ እንዲሰፍን ወደ ፈጣሪ እንመለስ” ፓስተር ታደሰ አዱኛ