በአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር በ183 የፈተና መስጫ ጣቢያዎች የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እየተሰጠ ነው።

27

እንጅባራ: ሰኔ 05/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር 8894 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ከዛሬ ሰኔ 5/2017 ዓ.ም ጀምሮ ክልላዊ ፈተና እየወሰዱ ነው።

የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ትምህርት መምሪያ ኀላፊ ደስታው አለሙ ፈተናው በ183 የፈተና መስጫ ጣቢያዎች እየተሰጠ መኾኑን ተናግረዋል። ፈተናውን የሚያሥተዳድሩ ከ550 በላይ የፈተና አሥፈጻሚዎች መመደባቸውንም ገልጸዋል።

በጸጥታ አካላት፣ በትምህርት መዋቅሩ፣ በኅብረተሰቡ እና በአሥተዳደር መዋቅር የጋራ ጥረት ለሁለት ቀናት ሲሰጥ የቆየው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሰላም መጠናቀቁን ያነሱት ኀላፊው ለ6ኛ ክፍል ፈተና ስኬታማነት የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩም ጠይቀዋል።

በጸጥታ ችግር ምክንያት ትምህርታቸውን ዘግይተው የጀመሩ 912 ተማሪዎች ደግሞ በቀጣይ የክልሉ ትምህርት ቢሮ በሚያወጣው መርሐ ግብር ፈተናቸውን የሚወስዱ ይኾናል ተብሏል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleሦስተኛው የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሀገር አቀፍ ኮንፈረንስ ዛሬም ቀጥሎ እየተካሄደ ነው።
Next articleየፈተና ጥሪ ማስታወቂያ