የዓለም አቀፉ የቤተሰብ ቀን ክልላዊ የማጠቃለያ መድረክ እየተካሄደ ነው።

12

ባሕር ዳር: ሰኔ 01/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ሴቶች ህፃናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ “የተሻሻለ የቤተሰብ ሥራና ገቢ ለሀገር ኢኮኖሚ” በሚል መሪ መልዕክት ክልላዊ የቤተሰብ ቀን የማጠቃለያ ዝግጅት እያካሄደ ነው።

በመድረኩ በአማራ ክልል ምክር ቤት የሴቶች ህፃናት ወጣቶችና ማኅበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አበራሽ ታደሰ እና ሌሎችም የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።

በቤተሰብ ቢዝነስ አጀማመር፣ የቤተሰብ ኢንተርፕራይዞችን ማስፋፋት፣ በቤተሰብ ግጭት አፈታት፣ የቤተሰብ የሥራ ባሕልና ተነሳሽነትን ማዳበር በሚሉ ርዕሰ ጉዳዩች ዙሪያ ውይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል።

ዘጋቢ:- አሰፋ ልጥገበው

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ትምህርት የአንድ ሀገር ሉዓላዊነት፣ ክብር እና ማንነት ማስጠበቂያ ነው” ሙሉነሽ ደሴ (ዶ.ር)
Next articleማኅበረሰቡ የራሱን ሰላም እንዲጠብቅ የሚያስችል ውይይት በደብረ ብርሃን ከተማ እየተካሄደ ነው።