ሕዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር የተቸገሩትን እና አቅመ ደካሞችን በማገዝ ሊኾን እንደሚገባ ሼህ ጀውሃር ሙሐመድ አሳሰቡ።

10

ባሕር ዳር: ግንቦት 29/2017 ዓ.ም (አሚኮ) 1 ሺህ 446ኛው የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል እየተከበረ ነው።

በበዓሉ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ጀውሐር ሙሐመድ ሕዝበ ሙስሊሙ አንድነቱን ማጠናከር እንደሚገባው ተናግረዋል።

በጎ ነገር ማድረግ የበዓሉ ቅድመ ሁኔታ መኾኑን ያነሱት ሼህ ጀውሐር ሙሐመድ ሕዝበ ሙስሊሙ የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓልን ሲያከብር የተቸገሩትን፣ አቅመ ደካሞችን እና የተፈናቀሉትን በመርዳት፣ የታመሙትን በመንከባከብ እንዲኾንም ነው ያስገነዘቡት።

እርድ ከሚፈጸመው አንድ ሦስተኛው ለምስኪኖች እንደሚለገስ ሃይማኖታዊ ግዴታ መኾኑንም ገልጸዋል። ከተማ አሥተዳደሩ ላበረከተው የመስገጃ ቦታ አመሥግነው ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ሁሉም ሕዝበ ሙስሊሙ እንዲተባበር አሳስበዋል።

ዘጋቢ፦ ዳግማዊ ተሰራ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous article1446ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ) በዓል በደብረ ብርሃን ከተማ ተከብሯል፡፡
Next article“ክልሉ ያለውን አቅም አሟጥጠን ስንጠቀም ዕድገት እና ብልጽግናን እናረጋግጣለን” አቶ ይርጋ ሲሳይ