1446ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ) በዓል በደብረ ብርሃን ከተማ ተከብሯል፡፡

14

ደብረ ብርሃን: ግንቦት 29/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የሃይማኖቱ ተከታዮችም ይህንን ታላቅ በዓል በኅብረት እና ምስኪኖችን በመዘየር እያከበሩ ስለመኾናቸው ተናግረዋል፡፡

የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ በድሉ ውብሸት ይህንን ታላቅ በዓል ስናከብር በፍፁም መዋደድ እና መረዳዳት መኾን ይገባዋል ብለዋል፡፡

የእርድ በዓል እንደመኾኑ መጠን ለበዓሉ የሚታረደውን ለአቅመ ደካሞች በማካፈል በፍቅር ማሳለፍ ይገባልም ብለዋል፡፡

የሃይማይኖቱ ተከታዮች ከሶላት እና ስግደት በኋላ የዚያራ መርሐ ግብር የሚያከናውኑ ሲኾን በበዓሉ አስተምህሮ መሰረት በዓሉን እያከበሩ ስለመኾናቸው ነው የተናገሩት፡፡

ዘጋቢ:- ደጀኔ በቀለ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleሙስሊሙ ማኅበረሰብ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ለመመለስ እየተሠራ እንደኾነ ምክትል ከንቲባ አስሜ ብርሌ ተናገሩ።
Next articleሕዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር የተቸገሩትን እና አቅመ ደካሞችን በማገዝ ሊኾን እንደሚገባ ሼህ ጀውሃር ሙሐመድ አሳሰቡ።