
ባሕር ዳር: ግንቦት 26/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር “ከብልጽግና ለብልጽግና” በሚል መሪ መልዕክት በከተማ አሥተዳደሩ ከሚገኙ መሪዎች ጋር ለኮሪደር ልማት የሚኾን የገቢ ማሰባሰቢያ የንቅናቄ መድረክ እየተካሔደ ነው።
በመድረኩ የአማራ ክልል መሬት ቢሮ ኀላፊ ሲሳይ ዳምጤ፣ የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው፣ የባሕር ዳር ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ሞላ ሲሳይን ጨምሮ ሌሎችም የከተማ አሥተዳደሩ እና የክፍለ ከተማ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን