የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ከፍተኛ ልዑክ ከሱዳኑ ጀኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ጋር ተገናኙ።

53

ባሕር ዳር: ግንቦት 25/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በብሔራዊ መረጃ እና ደህንት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀኔራል የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ከጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የተላከ መልዕክትን ለሱዳኑ ጄኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሀን አቀረቡ።

መልዕክቱን አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና የጠቅላይ ሚንስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማ‬ካሪ ጌታቸው ረዳ በፖርት ሱዳን ተገኝተው አቅርበዋል። ‪

በፖርት ሱዳን ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸው የገለፁት የልዑኩ መሪ “ሱዳን ሰላም እና መረጋጋቷን ለማረጋገጥ ለምታደርገው ጥረት ኢትዮጵያ የማይናወጥ ድጋፏን እንደምትቀጥል” በአጽንኦት መግለጻቸውን ተናግረዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ሰላም በአንድ ወገን አይመጣም” የአንጎት ወረዳ ነዋሪዎች
Next articleየገጠሩን ማኅበረሰብ አኗኗር ለማሻሻል የተጀመረው የገጠር ኮሪደር በሁሉም አካባቢዎች እየተስፋፋ መኾኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ተናገሩ።