“የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሀገር ግንባታ ተገቢውን አስተዋጽዖ እንድታበረክት መንግሥት የሚጠበቅበትን ሁሉ ይወጣል” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

14

ባሕር ዳር: ግንቦት 20/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ተወያይተዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዛሬ የኢዩቤልዩ ቤተ መንግሥትን ከጎበኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ተነጋግረናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሀገር ግንባታ ተገቢውን አስተዋጽዖ እንድታበረክት መንግሥት የሚጠበቅበትን ሁሉ እንደሚወጣ ገልጬላቸዋለሁ ነው ያሉት።

አዲስ ለተመደቡት ብጹአን አባቶች መልካም የሥራ ዘመንም ተመኝተዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleበኮምቦልቻ ከተማ ሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።
Next articleከ1 ሺህ 300 በላይ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተናን በበይነ መረብ እንደሚወስዱ የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር ገለጸ።