የኢ-ኮሜርስ የንግድ ዘርፍን ለማሳደግ እንደሚሠራ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።

7

አዲስ አበባ: ግንቦት 14/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕር እና በየብስ ላይ ያሉ የሎጀስቲክ ሥራዎችን በማዘመን እና ፈጣን በማድረግ የኢ-ኮሜርስ የንግድ ዘርፍን ለማሳደግ እንደሚሠራ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አስታውቋል። የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክ ሚኒስቴር የኢ-ኮሜርስ ሎጀስቲክ ዘርፍን ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በኅብረት እየሠራ መኾኑ ተገልጿል።

ኅብረቱን ለማሳደግም ከመንግሥት እና ከግል ተቋማት ጋር በትብብር ለመሥራት የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ለኢ-ኮሜርስ ሎጀስቲክ ተግዳሮት እና መፍትሔዎች ላይ ውይይት አካሂዷል። ለሀገር ዕድገት ሎጅስቲክ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው የጠቀሱት የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር ድኤታ ዴንዴ ቦሩ የታሰበውን የሀገር ብልጽግና ከፍ ለማድረግ የኢ-ኮሜርስ የንግድ አሠራር ወሳኝ ነው ብለዋል።

በቀጣይ የኢ-ኮሜርስ ሥራውን ይበልጥ ፈጣን እና የተቀናጀ ለማድረግ ሕጎችን እና የሎጅስቲክ አካሄዱን ለማስተካከል ሥራዎች እንደሚሠሩ ሚኒስትር ድኤታው ገልጸዋል። ኢ-ኮሜርስ በትልቅ ፍጥነት እያደገ እንዲመጣ መንግሥት ያሉ የሕግ ክፍተቶችን በማስተካል ኢ-ኮሜርስ የሥራ ዘርፍ ላይ ከተሰማሩ የግል እና የመንግሥት ተቋማት ጋር ሰፊ ኅብረት ሊያደርግ እንደሚገባም የንግዱ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

ዘጋቢ፦ ራሄል ደምሰው

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleየመንግሥት እና የሕዝብ ሀብት አጠቃቀም ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው፡፡
Next article“የዳኝነት ነጻነት ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ የሚያስችል የማዕዘን ድንጋይ ነው” የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ