በሰሜን ጎጃም ዞን ከአዴት ከተማ አሥተዳደር እና ይልማና ዴንሳ ወረዳ ነዋሪዎች ጋር ሕዝባዊ የሰላም ውይይት እየተካሄደ ነው።

76

ባሕር ዳር: ሚያዝያ 24/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በሰሜን ጎጃም ዞን ከአዴት ከተማ አሥተዳደር እና የይልማና ዴንሳ ወረዳ ነዋሪዎች ”የጥፋት እጆች እና መዘዞቹ” በሚል መሪ መልዕክት ሕዝባዊ የሰላም ውይይት እየተካሄደ ነው።

በውይይቱ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አሥተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኀላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ.ር)፣ የርእሰ መሥተዳድሩ የኢኮኖሚ አማካሪ ቀለመወርቅ ምህረቴ፣ የሰሜን ጎጃም ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አሰፋ ጥላሁን፣ የመከላከያ ሠራዊት በምሥራቅ ዕዝ የ304ኛ ኮር አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል አዲሱ ሙሐመድ እና ሌሎች የሥራ ኀላፊዎችም ተገኝተዋል።

በውይይቱ ኅብረተሰቡ ለሰላም እንዲረባረብ እና ችግሮች በውይይት ተፈተው ወደተሟላ ሰላም ስለሚገባበት ሁኔታ እንደሚመከር ይጠበቃል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous article“የተሠሩ የምርምር ሥራዎች በሰፊው ተመርተው ወደ ገበያ መቀላቀል አለባቸው” አሕመዲን መሐመድ (ዶ.ር)
Next articleየኮሌራ በሽታ አሁንም ትኩረት የሚሻው ጉዳይ ነው።