ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በባሕል፣ በኪነ ጥበብ እና ስፖርት ትብብራቸውን ለማጠናከር ይሰራሉ።

21

ባሕር ዳር: ሚያዚያ: 20/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የባሕል እና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂ ጋር በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። ውይይቱ የሁለቱን ሀገራት የባሕል፣ የኪነ ጥበብ እና ስፖርት ዘርፍ ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን አድርጓል።

በውይይቱ ኢትዮጵያ ካላት የብዝኅ ባሕል ባለቤት እና ታሪክ አንጻር ከሩሲያ ጋር በዘርፎቹ በጋራ መስራቷ ያለው አስፈላጊነት ተነስቷል።

ኢትዮጵያ ለብሪክስ አባል ሀገራት ባሕል እና የኪነ ጥበብ ሃብቷን ለማስተዋወቅ እንዲሁም የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን ለማጠናከር እያከናወነች ያለውን ሥራ የሩሲያ መንግሥት በመደገፍ በትብብር እንደሚሠራም ተገልጿል።

ሁለቱ ወገኖች በቀጣይ የጋራ የመግባቢያ ስምምነት በመፈራረም የሀገራቱን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከር መስማማታቸውን የባሕል እና ስፖርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ያሠለጠናቸው 33ኛ ዙር ምልምል የፓሊስ አባላት ጎንደር ከተማ ሲገቡ አቀባበል ተደረገላቸው።
Next article8 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 151 አልሚ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን የሰሜን ወሎ ዞን አስታወቀ።