የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

129

ባሕር ዳር:ሚያዝያ 16/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ደረጃ (6ኛ ክፍል) እና የመካከለኛ ደረጃ (8ኛ ክፍል) ማጠናቀቂያ ስርትፊኬት ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።

የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ደረጃ (6ኛ ክፍል) እና የመካከለኛ ደረጃ (8ኛ ክፍል) ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና በሁለት ዙር ፈተናውን ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ መኾኑንም ተገልጿል።

የመጀመሪያ ዙር ፈተና የመጀመሪያ ደረጃ (6ኛ ክፍል) ከሰኔ 05 እስከ 06/2017 ዓ.ም እና የመካከለኛ ደረጃ (8ኛ ክፍል) ከሰኔ 03 እስከ 04/2017 ዓ.ም ፈተና መስጫ ቀናት እንዲሆን ተወስኗል ተብሏል።

በየደረጃው የሚገኙ የትምህርት ተቋማት ከራሳቸው ተጨባጭ ሁኔታ በመነሳት ተፈታኝ ተማሪዎችን በአግባቡ በማዘጋጀት፣ በቅድመ ፈተና፤ በፈተና ወቅት እና በድህረ ፈተና መከናወን ያለባቸውን ዝርዝር ተግባራት ከወዲሁ በመለየት እና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ተግባራትን እንዲያከናውኑ አሳስቧል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleበድጋሜ የወጣ የቋሚ ቅጥር ማስታወቂያ
Next article“ዜጎችን በተሻለ የሕይዎት ደረጃ እና ጤንነት እንዲኖሩ ከማድረግ የበለጠ ምንስ ሰብዓዊነት አለ” ለገሰ ቱሉ (ዶ.ር)