ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በፖፕ ፍራንሲስ ህልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ።

72

ባሕር ዳር: ሚያዚያ: 13/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሮም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪ በኾኑት በብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ፍራንሲስ ህልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል።

ፓትሪያርኩ ለመላው የሮማ ካቶሊካዊ መሪዎች እና በመላው ዓለም ላሉ ምእመናን እንዲሁም በኢትዮጵያ ላሉ ካቶሊካውያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስም ሃዘናቸውን መግለጻቸውን ከኢኦተቤ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በፖፕ ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ።
Next articleየፈተና ጥሪ