ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በፖፕ ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ።

66

ባሕር ዳር: ሚያዚያ 13/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት በርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፖፕ ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እገልጻለሁ ብለዋል። ነፍሳቸው በሰላም እንድታርፍም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የእርሳቸው መልካም ሥራ እና የአገልግሎት ትሩፋት ትውልዶችን ማነሳሳቱን እንደሚቀጥልም አመላክተዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ አረፉ።
Next articleየጠቅላይ ሚኒስትሩ የቬይትናም ጉብኝት የሀገራቱን ግንኙነት የሚያጠናክር እና ተሞክሮ የተቀሰመበት ነው።