የአማራ ልማት ማኅበር 15ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።

31

ባሕር ዳር:ሚያዝያ 07/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ልማት ማኅበር (አልማ) “በራስ አቅም የመልማት ምልክት” በሚል መሪ መልዕክት ጠቅላላ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።

በጠቅላላ ጉባዔው የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፉዬ፣ ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)፣ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኀላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ.ር) እና ሌሎችም ከፍተኛ መሪዎች ተገኝተዋል።

አልማ “በራስ አቅም የመልማት ምልክት” በሚል ዋና መልእክቱ ሁሉን አቀፍ በኾኑ የሕዝብ የልማት ሥራዎች ላይ የሚሠራ ማኅበር ነው።

ማኅበሩ በዛሬው 15ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤው አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴው እንደሚገመገም ተገልጿል። ለማኅበሩ አሻራቸውን ላበረከቱ ተቋማትም እውቅና እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሀኖይ ቬይትናም ይፋዊ ጉብኝት በማድረግ ላይ ይገኛሉ።
Next articleየፍትሐ ብሔር እና የወንጀል ሕግ አንድነት እና ልዩነት፦