በሕገወጥ መንገድ ወደሌላ አካባቢ ሊዘዋወር የነበረ ተሽከርካሪ በቁጥጥር ስር ዋለ።

42

ባሕር ዳር: ሚያዝያ 03/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር በዳንግላ ከተማ በሕገወጥ መንገድ ከላይ ከሰል በመጫን በስር የተፈታ የመንግሥት ተሽከርካሪ ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ተሽከርካሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን የከተማ አሥተዳደሩ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

የዳንግላ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ጀጃው ሞላ (ኢ.ር) እንደገለጹት በታጠቁ ኀይሎች አማካኝነት የመንግሥት ተሽከርካሪው ከአፈሳ ወደ በሕርዳር ሲጓዝ ነው በአካባቢው ማኅብረሰብ በተሰጠው ጥቆማ በቁጥጥር ስር የዋለው።

የከተማ አሥተዳደሩ የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ተወካይ ኀላፊ ብርሃኑ ገድፍ የአካባቢው ማኅበረሰብ እነዚህን እና መሰል ወንጀሎች ሲፈጠሩ ጥቆማ መስጠት እንዳለበት ማሳሰባቸውን የዳንግላ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleየፈለገ ሕይዎት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለዐይን ሞራ ግርዶሽ ህክምና ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መኾኑን አስታወቀ።
Next articleየሕዝብ አጀንዳዎችን ነቅሰው ማውጣታቸውን የምክክሩ ተሳታፊ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተናገሩ።