በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአማራ ክልል የባለድርሻ አካላት ክልላዊ የምክክር መድረክ ተጀመረ።

91

ባሕር ዳር: ሚያዝያ 02/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአማራ ክልል አጀንዳ የማሠባሠብ ሥራውን እያከናወነ ነው።

የወረዳ ማኅበረሰብ ተወካዮች የአጀንዳ ማሠባሠብ እና ለአጠቃላይ የምክክር ጉባኤው ወኪሎችን የመምረጥ ሥራ መጋቢት 01/2017 ዓ.ም መጠናቀቁ ይታወሳል።

መጋቢት 02/2017 ዓ.ም ደግሞ አምስት ባለድርሻ አካላትን ያካተተው ክልላዊ የምክክር መድረክ ተጀምሯል።

ዛሬ በምክክር ሂደቱ ላይ የተገኙት አምስቱ ባለድርሻ አካላትም፡-

👉የመንግሥት ተቋማት ተወካዮች

👉መንግሥታዊ ያልኾኑ ተቋማት እና ማኅበራት ተወካዮች

👉የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች

👉ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እና

👉 በመጀመሪያው ዙር ምክክር ለሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የተመረጡ የወረዳ ማኅበረሰብ ወኪሎች ናቸው።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleዜጎች ፈተና ሳይበግራቸው ትልቁን ምስል አሳይተዋል።
Next article“የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አንዱን ጥሎ ሌላውን አንጠልጥሎ የሚሄድበት አሠራር የለውም” ኮሚሽነር መላኩ ወልደማርያም