በእደ ጥበብ ሥራ ተጠቃሚ መኾናቸውን በጎንደር ከተማ በሴፍትኔት መርሐ ግብር ታግዘው ወደ ሥራ የገቡ ተጠቃሚ ሴቶች ገለጹ።

30

ጎንደር: ሚያዝያ 01/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በጎንደር ከተማ በሴፍትኔት መርሐ ግብር በእደ ጥበብ ሥራ ላይ የተሠማሩ ሴቶች ጥጥ በመፍተል፣ ባሕላዊ አልባሳትን በማዘጋጀት እና ስፌት በመሥፋት ተጠቃሚ መኾናቸውን እትጌ ሙሉጌታ ተናግረዋል።

የእደ ጥበብ ሥራው የገቢ ምንጭ በመኾን ሕይዎታቸውን እየለወጠ መኾኑን ያነሱት ደግሞ ወይዘሮ ሰላም ሽመልስ ናቸው።

የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ምግብ ዋስትና እና ሴፍትኔት ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ሀድያ መሐመድ በዘርፉ ከ300 በላይ ሴቶች ተጠቃሚ መኾናቸውን ገልጸዋል።

ሴቶቹ በዓመት ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ በመቆጠብ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ እንደቻሉም ነው ያብራሩት።

ዘጋቢ – ያየህ ፈንቴ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous articleፍትሕን ፍለጋ የሚንከራተት ማኅበረሰብ ሊኖር እንደማይገባ የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ አሳሰበ።
Next articleከ51 ሺህ በላይ የማኅበረሰብ ክፍሎችን በሴፍትኔት መርሐ ግብር ተጠቃሚ ማድረጉን የጎንደር ከተማ አሥተዳደር አስታወቀ።