በአማራ ክልል ነገ የሀገራዊ ምክክር አጀንዳዎችን የማሰባሰብ ሥራ ይጀመራል።

27

ባሕር ዳር: መጋቢት 26/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአማራ ክልል ከነገ ጀምሮ የሚያደርገውን የአጀንዳ ማሠባሠብ ሥራ አስመልክቶ መግለጫ እየሰጠ ነው።

መግለጫውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ.ር) እና ኮሚሽነር መላኩ ወልደማርያም እየሰጡ ነው።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአማራ ክልል ከነገ መጋቢት 27/2017 ዓ.ም ጀምሮ አጀንዳ ያሠባሥባል።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር መላኩ ወልደማርያም ለጋራ ሀገር በጋራ መሥራት አለብን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአማራ ክልል የተለያዩ ሥራዎችን ሲሠራ መቆየቱንም ተናግረዋል።

ኮሚሽኑ የተሳታፊ ልየታ ማጠናቀቁን ተከትሎ ከነገ ጀምሮ የአጀንዳ ማሠባሠብ ሥራውን ይቀጥላል ነው ያሉት።

ወኪሎች በተገኙበት የአጀንዳ ማሠባሠብ ሥራው ነገ ጀምሮ ለቀናት ይቆያል ነው ያሉት። ተሳታፊዎች ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበተሠሩ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎች የተራቆቱ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገግሙ ማድረግ መቻሉን የምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ነዋሪዎች ተናገሩ።
Next articleበየሁለት ሰከንዱ አንድ ሰው የሚቀጥፈው በሽታ!