የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር የዒድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ የማዕድ ማጋራት ሥነ ሥርዓት አካሄደ።

31

አዲስ አበባ: መጋቢት 21/2017 ዓ.ም (አሚኮ) 1 ሺህ 446ኛውን የዒድ አልፈጥር በዓል ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ ከተማ የማዕድ ማጋራት ተካሄዷል።

የማዕድ ማጋራቱ በከተማው ሁሉም ክፍለ ከተሞች ባሉ የምገባ ማዕከላት ተካሂዷል።

በቦሌ ክፍለ ከተማ በተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል በመገኘት የማዕድ ማጋራት ያካሄዱት የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አበቤ ለ1 ሺህ 446ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አሥተላልፈዋል።

በረመዳን ወርም ገቢያቸው ዝቅተኛ ለኾኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች ምገባ መካሄዱን ተናግረዋል።

ዘጋቢ፦ ተመስገን ዳረጎት

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም መጠናቀቁን የፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።
Next articleየአድማ መከላከል አባላት በኮኪት ከተማ አቀባባል ተደረገላቸው።