“መንግሥት ለትምህርት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)

26

ባሕር ዳር: መጋቢት 11/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በተገኙበት 6ኛ ዙር፣ 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 21ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያሄደ ነው፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄዎችን እና አስተያየት አቅርበዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በማብራሪያቸውም በየአካባቢው የምንጋዋቸው ሰዎች አትማሩ፣ አትታከሙ፣ አትረሱ ከሚሉ ጋር ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡

የምንዋጋቸው መድኃኒት አውጥተው የሚደፉ፣ ማዳበሪያ እንዳይደርስ የሚያደርጉ ነገር ግን ለሕዝብ የሚታገሉ ናቸው ብለዋል፡፡ ትምህርት ምን ያደርግላቸዋል ብለው የሚያስቡ ናቸው ነው ያሉት፡፡

በጩኸት እና በግርግር እውነት ለመደበቅ የሚደረግ ሙከራ ስላለ በዜጎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያመጣ መኾኑን ነው የተናገሩት፡፡ መንግሥት ለትምህርት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መኾኑንም ገልጸዋል፡፡

በጤናው ዘርፍም በትኩረት እየተሠራ መኾኑን አንስተዋል፡፡ ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው የመመለስ ሥራ እንደሚሠራም ተናግረዋል፡፡

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous article“በቀን 150 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያ ከወደብ እናጓጉዛለን” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)
Next article“በምርት ዘመኑ 187 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዶ እየተሠራ ነው” ድረስ ሳህሉ (ዶ.ር)