ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ነው።

33

ባሕር ዳር: መጋቢት 11/2017 ዓ.ም (አሚኮ)ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ እና ማብራሪያ፦

✍️ “በግብርና ምርት የአነስተኛ አርሶ አደሮች የሰብል ሽፋን 20 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር ደርሷል፤

✍️ በበጋ መስኖ ልማት 3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በስንዴ ተሸፍኗል፣

✍️ በዚህም ከ300 ሚሊየን ኩንታል ያላነሰ ምርት ይስበሰባል ተብሎ ይጠበቃል፤

✍️ በቡና እና ሻይ ምርትም የተሻለ ስኬት ተመዝግቧል፤

✍️ ባለፉት ስምት ወራት ብቻ ከቡና ወጪ ንግድ 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፤

✍️ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት የሰብ ሰሃራ ዕድገት 4 ነጥብ 2 ይኾናል ብለው ገምተው ነበር፤

✍️ ኢትዮጵያ 8 ነጥብ 4 በመቶ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ችላለች፤

✍️ የአነስተኛ አርሶ አደሮች የሰብል ሽፋን ከ17 ነጥብ 5 ሚሊዮን ወደ 20 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር ማደግ ተችሏል፤

✍️ ዛሬ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛ ስንዴ አምራች ሀገር ነች፤

✍️ በስንዴ ብቻ ሳይኾን በሌሎችም ዘርፎች የመጣው እምርታ ይበል ይቀጥል የሚያስብል ነው፤

✍️ ለምሳሌ ቡና በለውጡ ማግስት 700 ሚሊዮን ገደማ በዓመት ኤክስፖርት እናደርግ ነበር፤ በቡና ኤክስፖርት ባለፉት ስምንት ወራት ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘት ተችሏል፤

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የ8 ወራት የሥራ አፈጻጸሙን እየገመገመ ነው።
Next article3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገደማ የዕዳዳ ሸግሽግ መገኘቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ተናገሩ።