የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በተገኙበት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 21ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያሄደ ነው፡፡

46

ባሕር ዳር: መጋቢት 11/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄዎችን እና አስተያየት እያቀረቡ ነው፡፡ የምክር ቤት አባላቱ ያነሷቸው ጥያቄዎች እና አስተያያቶች፡-

👉 ኢትዮጵያ ያገጠሟት ችግሮች ፖለቲካ ወለድ ናቸው፤ መፍትሔያቸውም ፖለቲካዊ እንጂ ግጭት አይደለም፡፡

👉 በመደማመጥ እና በሰጥቶ መቀበል ላይ ተመሥርቶ ሰላምን ማምጣት ይገባል፡፡

👉 ባለፉት ዓመታት ግጭቶች እና ጦርነቶች ሰዎች ተጎድተዋል፡፡

👉 በጦርነት ምክንያት የሀገር ሀብት እየወደመ ነው።

👉 በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል ያልተቋረጡ ግጭቶች ቀጥለዋል፡፡ ግጭት እና አለመረጋጋት ብዙዎች ለችግር እንዲጋለጡ አድርጓል፡፡

👉 የኑሮ ውድነት ለዜጎች ፈተና ኾኗል፤ ከዚህ ላይ ያለው ግጭት ደግሞ የኑሮ ውድነቱ እንዲባባስ አድርጓል፡፡

👉 የፍትሕ ሥርዓቱ አሁንም ችግር አለበት፤ ከግጭት አዙሪት ካልወጣን ሀገራችን አደጋ ውስጥ እንጥላለን

👉 በአማራ ክልል እና በአሮሚያ ክልል ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ኀይሎች የሰላም ጥሪውን መቀበል አለባቸው፡፡ ለሰላምም ተባባሪ መኾን መቻል አለባቸው

👉 የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ሕዝብ በላቡ የገነባውው የትብብር እና የኅብረት ምሳሌ ነው፣ የአይበገሬነታችንም ምልክት ነው፡፡

👉 የሕዳሴው ግድብ ግንባታ ሙሉ ለሙሉ ለማጠናቀቅ ምን ያክል ጊዜ ይቀረዋል?

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሕዝብ ተወካዮች ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ነው።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleመንግሥት ያጋጠሙ ችግሮችን በመፍታት ተማሪዎች እንዲመለሱ ማድረግ ያልቻለው ለምንድን ነው?
Next articleየምክር ቤት አባላቱ በሰላም ጥሪዎች እና በኑሮ ውድነት ላይ አተኩረው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄዎችን አቅርበዋል።