ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ነገ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ።

30

ባሕር ዳር: መጋቢት 10/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ነገ መጋቢት 11 2017ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመገኘት ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሏል።

ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው የፌዴራል መንግሥት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የአፈጻጸም ሪፖርትን መነሻ በማድረግ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ነው ምላሽና ማብራሪያ የሚሰጡት።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የጣና ዳር ንግሥቷ፣ ባለዘንባባዋ ሙሽራ፣ የቱሪዝም አስኳሏ ባሕር ዳር ሥራ ላይ ነች” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Next articleበሳይንስ ዘርፍ የሴት ተመራማሪዎችን ተሳትፎ ለማሳደግ እየሠራ መኾኑን የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ገለጸ።