ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ልማቶችን ጎበኙ።

19

ባሕር ዳር፡ መጋቢት 06/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በላይ አርማጭሆ ወረዳ እየተሠሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ.ር)፣ የርዕሰ መስተዳድሩ የኢኮኖሚ ጉዳዮች አማካሪ ቀለመወርቅ ምኅረቴ፣ የርዕሰ መሥተዳድሩ የመሰረተ ልማት አማካሪ ደሴ አሰሜ፣ የአማራ ክልል መንገድ ቢሮ ኃላፊ ጋሻው አወቀ (ዶ.ር)፣ እና ሌሎች አመራሮችም ተገኝተዋል።

አመራሮቹ በሌማት ትሩፋት፣ በእንስሳት እርባታና በወተት ተዋፅኦ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት እና ሌሎችንም የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን መረጃ እንደሚያመለክተው በተፈጥሮ ሀብት ልማት ሥራ እየተከናወኑ ያሉ የተፋሰስ ልማት ሥራዎችንም ጎብኝተዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በጎንደር ከተማ ነዋሪውን ተጠቃሚ ያደረጉ 56 የልማት ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልገሎት በቅተዋል” ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው
Next articleየጣና ሐይቅ ብዝኃ ሕይዎትን በቅንጅት በመጠበቅ አዎንታዊ ለውጥ ማምጣቱን የጣና ሐይቅ እና ሌሎች ውኃማ አካላት ጥበቃ እና ልማት ኤጀንሲ ገለጸ።