በአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ለሚገኙ ሴት መሪዎች የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና እየተሰጠ ነው።

9

እንጅባራ፡ መጋቢት 02/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ለሚገኙ ሴት መሪዎች የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና እየተሰጠ ነው።

ሥልጠናውን የአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ሴቶች፣ ሕጻናት እና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ ከብሔረሰብ አሥተዳደሩ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት እና ከእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ያዘጋጁት ነው።

በሥልጠናው በአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ከሁሉም ወረዳዎች እና ከተማ አሥተዳደሮች የተውጣጡ ሴት መሪዎች ተገኝተዋል።

የሴቶች የመሪነት ሚና ሥርዓተ ጾታ እና የሥራ ፈጠራ የሚሉ ርዕሰ ጉዳዮችም ሥልጠናው ያተኮረባቸው ጉዳዮች ናቸው።

የሥልጠናው ተሳታፊዎችም ሥልጠናው ሥራ ፈጣሪ እና ጠንካራ ሴት መሪዎችን ለመፍጠር አቅም የሚፈጥር መኾኑንም ተናግረዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በደሴ እና በኮምቦልቻ ከተሞች የልማት ሥራዎችን ይጎበኛሉ።
Next articleአርብ ገብያ – ሰከላ – ቲሊሊ አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን አስፋልት ወደ ማንጠፍ ሥራ መጀመሩን የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር ገለጸ።