ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ሆራይዘን አዲስ ጎማ ማኑፋክቸሪንግን ጎበኙ።

38

ባሕር ዳር: የካቲት 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት የበላይ ጠባቂ የኾኑት ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሆራይዘን አዲስ ጎማ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበርን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ፕሬዝዳንቱን ጨምሮ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ዴዔታ እንዳለው መኮንን፣ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ጀማል አሕመድ እና የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ቴዎድሮስ መብራት ተሳትፈዋል።

በጉብኝታቸውም የሆራይዘን አዲስ ጎማ ማኑፋክቸሪንግን የሥራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው መመልከታቸውን ኢዜአ መረጃ ያሳያል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበምርት ዘመኑ ከ200 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተፈጥሮ ማዳበሪያ እንደሚሸፈን የሰሜን ሸዋ ዞን አስታወቀ።
Next articleበኮምቦልቻ ከተማ የኢንዱስትሪ እና የፋይናንስ ኤክስፖ ሊካሄድ ነው።